በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ስራዎች ተስፋ ሰጪ ስኬቶች ተመዝግበዋል ( አቶ ጥላሁን አባይ)

ኢኢቢ: ጥር 13/ 2017 ዓ.ም (ባህርዳር) የኢዱስትሪ ሚኒስቴር የ2017 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀሙን ለክልልና ከተማ አስተዳደር ፣ ተጠሪ ተቋማት፣ ባለ ድርሻ አካላትና የዘርፍ ማህበራት አቅረቦ እየገመገመ ነው ።

የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ያቀረቡት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ አቶ ጥላሁን አባይ እንደገለፁት መንግስት ለዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት፣ በተሰሩ ቅንጅታዊ ስራዎችና ድጋፎች የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም አጠቃቀም ከአለፉት ዓመታት ጋር ሲነፃፀር የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ ተችሏል፡፡

ዋና ዋና በሆኑ የስራ ማሳያዎች እንደ ውጭ ምንዛሬ ግኝት፣ ተኪ ምርት፣ የአቅም አጠቃቀም፣ የግብዓት አቅርቦትና ሌሎች የዘርፉ ስራዎች ተስፋ ሰጪ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልፀዋል።

በሌላ በኩል በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በፋይናስ በአቅም ግንባታ ፣ በመሰረተ ልማትና በምርምር ስኬታማ ስራዎች በመስራቱ የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ መቻሉን የገለፀፁት አቶ ጥላሁን የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት አፈፃፀም ከ2016 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር ከፍ ያለ መሆኑን ጠቁመዋል ።

ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት!!

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

Facebook- https://www.facebook.com/investamhara?mibextid=ZbWKwL

Website- http://www.investinamhara.gov.et/

YouTube- youtube.com/channel/UCRKHHaX4S9KHqNVhLAt1bkg

WhatsApp- https://chat.whatsapp.com/C7sUyLeKQ5D9C4kLK4Uizo

Twitter- https://x.com/amhara_and77292

TikTok- https://www.tiktok.com/@investamhara.regi?_t=8rw4bEMf3hg

May be an image of 7 people and dais

See insights and ads

Boost post

All reactions:

12Ermias Mekonnen and 11 others

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top