ሰሜን ምዕራብ አማራ ኢንዱስትሪ ልማት ቀጠና
- ይህ የኢንዱስትሪ ልማት ቀጠና የሰ/ጎንደር፣የምዕ/ጎንደር፣ጎንደር ከተማ እና ከፊል የማዕከላዊ ጎንደር ዞኖችን የሚያካልል ነው፡፡
- አካባቢው በተለይ በምዕ/ጎንደርና ከፊል ሰሜን ጎንድር ከፍተኛ የሆነ የቅባትና የጭረት ምርቶች (ሰሊጥ፣ሱፍ፣በሎቄ፣ጥጥ፣…ወዘተ) እና ሰፊ የእንሰሳት ሀብት ያለው፣ በጎንደር ከተማና ሰ/ጎንደር ደግሞ በዩኔስኮ የተመዘገቡ ሰፊ የቱሪስት መስህብ ሀብቶች ያሉበት ቀጠና ነው፤
- ለአብነት ሰሜን ብሔራዊ ፓርክ፣የአፄ ፋሲለደስ ቤተ-መንግስት ፣አላጥሽ ብሔራዊ ፓርክ እና ፣እንደ ዋሊያ አይቤክስና ጭላዳ ባቡን ያሉ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ብርቅ እንሰሳት…የሚገኙበት ነው፡፡
- ስለሆነም ፡-
- ዘመናዊ የቅባት እህሎችና ጥጥ ማምረት
- የሆቴልና ቱሪዝም ስራዎች
- እንሰሳት እርባታና ማድለብ
- አግሮፕሮሰሲንግና ቴክስታይል በቀጠናው ቅድሚያ የሚሰጣቸው የኢንቨስትመንት ዘርፎች ናቸው፡፡