*******************************************
ኢኢቢ: ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም: ባህር ዳር
የዩኒሰን ሆቴል እህት ኩባንያ የሆነውና ከተቋቋመ 3 ዓመት ገደማ የሆነው ዩኒሰን ዘይት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚከበረውን መጭውን የገና በዓል ታሳቢ በማድረግ የማምረት አቅሙን ማሳደጉን የፋብሪካው ጀነራል ማናጀር አቶ አሻግሬ ጌትነት ለአሚኮ ሚዲያ ኮርፖሬሽንና ለክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ገልፀዋል፡፡ ጀነራል ማናጀሩ እንደገለፁት ፋብሪካው ቀደም ሲል በቀን 60,000 ሊትር ዘይት ሲያመርት የቆየ መሆኑን ገልፀው አሁን ላይ በዓሉን ታሳቢ በማድረግ 90,000 ሊትር ዘይት በማምረት ለተጠቃሚው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ እየተደረገ መሆኑንና ያለውን የኑሮ ውድነቱን በማረጋጋት በኩል ፋብሪካው ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አቶ አሻግሬ ጌትነት አብራርተዋል፡፡ ድርጅቱ ከዘይት ምርቱ በተጨማሪ የአኩሪ አተር ተረፈ ምርት ወደ አውሮፓ ገቢያ (ፓኪስታን) ኤክስፖርት በማድረግ የውጭ ምንዛሬ ለሀገሪቱ በማስገኘት በኩል መልካም ጅምር እንቅስቃሴ መኖሩን ከፋብሪካው ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ ፋብሪካው ለ250 ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል ፈጥሯል፡፡
ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት!!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
Facebook- https://www.facebook.com/investamhara?mibextid=ZbWKwL
Website- http://www.investinamhara.gov.et/
YouTube- youtube.com/channel/UCRKHHaX4S9KHqNVhLAt1bkg
WhatsApp- https://chat.whatsapp.com/C7sUyLeKQ5D9C4kLK4Uizo
Twitter- https://x.com/amhara_and77292