***************************************
ኢኢቢ: ታሕሣሥ 18፣ 2017 (ባህርዳር ) ከሐምሌ 1 ቀን 2016 ጀምሮ በአማራ ክልል 163 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 940 አልሚዎች ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ፡፡
ፈቃድ የተሰጣቸው አልሚዎች ወደ ስራ ሲገቡ ለ20 ሺህ 368 ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩ ቢሮው ለፋና ዲጂታል ገልጿል።
አልሚዎቹ በአግሮፕሮሰሲንግ፣ ጨርቃጨርቅ፣ ኬሚካል፣ ኮንስትራክሽን፣ እንጨትና ብረታብረት፣ ቱሪዝም፣ አበባ ልማት፣ ግብርና እና ሪልስቴትን ጨምሮ በሌሎች መስኮች እንደሚሰማሩ ቢሮው አብራርቷል፡፡
በክልሉ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የኢኮኖሚ ድርሻም 8 ነጥብ 5 መሆኑን ነው ቢሮው ያስታወቀው፡፡
የኢንቨስትመንት ፍሰቱ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንጻር የ62 ቢሊየን ብር ጭማሪ ማሳየቱም ተጠቅሷል፡፡
በሌላ በኩል 62 አዲስ ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት መግባታቸውን እና ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ49 ጭማሪ አሳይቷል ተብሏል፡፡ ኤፍ ቢ ሲ እንደዘገበው



See insights and ads
All reactions:
13Gashaw Awoke – ጋሻው አወቀ and 12 others