************************************
ኢኢቢ፡ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም፡ ባህርዳር
በደቡብወሎ ዞን ኩታበር ወረዳ የደቡብ ወሎ ዞን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ተወካይ ኃላፊ አቶ አሰራር አደም፤ የደቡብ ወሎ ዞን የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ኃላፊና የከተማ ክላስተረ አስተባባሪ አቶ መርከቡ ታረቀኝ፤ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል ይመር፤ ከዞን አስከ ወረዳ የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት አመራሮች ፤የማጅመንት ኮሚቴ አባላት ፤አጋር አካላት እንዲሁም ባለሀብቶች በተገኙበት የኢትዮጵያ ታምርት ፎረም ተካሄዷል፡፡
በመድረኩ ላይ አጠቃላይ የወረዳው የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በወረዳው ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አህመዱ ሰይድ ቀርቦ ሰፊና ጥልቅ ውይይት የተደረገበት ሲሆን እየገጠሙ ያሉ ችግሮች በሚፈቱበት መንገድ ላይም በመድረኩ በተሳተፉ ባለሀብቶችና በአጋር አካላት ሰፊ ሀሳብ ቀርቦ ውይይት ተደርጎ መተማመን ላይ መድረስ ተችሏል፡፡
‹‹ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት››
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
Facebook- https://www.facebook.com/investamhara?mibextid=ZbWKwL
Website- http://www.investinamhara.gov.et/
YouTube- youtube.com/channel/UCRKHHaX4S9KHqNVhLAt1bkg
WhatsApp- https://chat.whatsapp.com/C7sUyLeKQ5D9C4kLK4Uizo
Twitter- https://x.com/amhara_and77292
TikTok- https://www.tiktok.com/@investamhara.regi?_t=8rw4bEMf3hg…