ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የአማራ ክልል “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብርን አስጀመሩ።
ኮምቦልቻ፣ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም (ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ)
ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በኮምቦልቻ ከተማ ተገኝተው አራተኛውን የአማራ ክልል “ኢትዮጵያ ታምርት” ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብርን አስጀምረዋል።
አራተኛው የአማራ ክልል “ኢትዮጵያ ታምርት” ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር “ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት” በሚል መሪ መልዕክት ነው መካሄድ የጀመረው።
በማጠቃለያ መርሐ ግብሩ ከርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በተጨማሪ ሌሎች ከፍተኛ የክልል እና የፌዴራል ከፍተኛ መሪዎች ተገኝተዋል።
በአማራ ክልል “ኢትዮጵያ ታምርት” ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር ኢንዱስትሪዎች ምርቶቻቸውን የሚያስተዋውቁበት፣ ልምድ የሚለዋወጡበት እና የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት ኤክስፖ ተዘጋጅቷል። በኤክስፖው 145 አምራች ኢንዱስትሪዎች እየተሳተፉ ነው።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅማቸው እንዲጨምር አድርጓል። እንደማነቆ የሚያነሷቸው ችግሮችም እንዲፈቱ እያደረገ ነው።
ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት!!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
Facebook- https://www.facebook.com/invpestamhara?mibextid=ZbWKwL
– http:/www.investinamhara.gov.et/
YouTube- youtube.com/channel/UCRKHHaX4S9KHqNVhLAt1bkg
ፈኀWhatsApp- https://chat.whatsapp.com/C7sUyLeKQ5D9C4kLK4Uizo
Twitter- https://x.com/amhara_and77292
TikTok- https://www.tiktok.com/@investamhara.regi?_t=8rw4bEMf3hg…
See less

