ርዕይ፣ተልዕኮ፣እሴቶችና የአሠራር መርሆዎች፣የሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት/ግቦች/

በ 2022 የክልሉ ኢኮኖሚ በኢንዱሰትሪ ላይ የተመሰረተ ሆኖ ማየት፡፡

ተልዕኮ፡

  • የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስፋትና የዘርፉን ማነቆዎች በመለየት ለመፍትሄ የሚረዱ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎቸን በመቀመርምቹ የሆነ የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት መሰረቱን በማስፋት የኢንቨስትመንት ፍሰቱን ማሳደግ፣
  • የክልሉን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ልማት የሚደገፉ ተቋማትን አቅም በመገንባትና በቴክኖሎጂ በመደገፍ የዘርፉን ፈጣን ልማትና ቀጣይነት ማረጋገጥና የክልሉን ኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ማፋጠን፣
  • የአምራች ኢንዱስትሪዎች ውጤት የሆኑ ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት መተካት፣
  • አምራች ኢንዱስትሪዎችና የግብርና ኢንቨስትመንት የኤክስፖርት ምርትን በማምረት የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ማሳደግ፣
  • በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች ዘመናዊና ተወዳዳሪ የሆነ የአሰራር ስርዓትን ተከትለው የዘርፉን ልማት እንዲያስፋፉ በመደገፍ ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር፣ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ፡፡
  • የላቀ አገልግሎት፣
  • የደንበኛ እርካታ፣
  • ጥራትና ቅልጥፍና፣
  • የስራ ፍቅርና ከበሬታን፤
  • አገልጋይነት፣
  • ቅንጅታዊ አሰራር
  • ዘመናዊነት
  • ዝግጁነት
  • ፈጣሪነት
  1. የአመራሩንና የፈጻሚዎችን አቅም ማሳደግ
  2. የተገልጋዮችን እርካታና አመኔታ ማሳደግ
  3. የሃብት አጠቃቀምንና ውጤታማነትን ማሳደግ
  4. የክልሉን ጸጋዎች በማስተዋዎቅ የኢንቨስትመንት ፍሰቱን በማሳደግ፤ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ እንዲያወጡ ማድረግ
  1. ለአምራች ኢንዱስትሪዎችና ለሌሎች ለኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የሚውል የመሬት፣  የመሰረተ ልማትና የፋይናንስ አቅርቦትን ማሳደግ
  1. የአምራች ኢንዱስትሪዎችና ሌሎች የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የማበረታቻ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በመደገፍ ወደ አፈጻጸም የመግባት አቅማቸውን ማሳደግ፣
  1. የአምራች ኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ማሳደግ
  2. በአምራች ኢንዱስትሪዎች እና በሌሎች የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የሚገኝ የኤክስፖርት ገቢ ማሳደግ
  1. ስትራቴጂክ የገቢ ምርትን የሚተኩ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የሀገር ውስጥ የገበያ ድርሻን ማሳደግ፣
  1. ከአምራች ኢንዱስትሪዉ እና ከሌሎች የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የሚፈጠረውን የስራ እድል ማሳደግ
  1. የአምራች ኢንዱስትሪዎችንና ሌሎች የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ምርታማነት የሚያሻሽሉ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ማሳደግ፣
  1. የቴክኖሎጅ ልማትና የመረጃ አያያዝ ውጤታማነትን ማሳደግ
Scroll to Top